የፀሐይ ኢንሹራንስ አ.ማ
Tsehay Insurance S.C
እጩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላትን ጥቆማ ለመቀበል የወጣ ማስታወቂያ
የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምርጫ ለማከናወን እንዲቻል የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ እና የኩባንያው የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ጥቆማ እና ምርጫ አሰራር ደንብ መሰረት የቦርድ አባላት የምልመላና አስመራጭ ኮሚቴ በኩባንያው የባለአክሲዮኖች 11ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ታህሳስ 01 ቀን 2015 ዓ.ም መመረጡ ይታወሳል፡፡
በዚሁ መሰረት የተሰየመው የቦርድ አባላት የምልመላና አስመራጭ ኮሚቴ የዳይሬክተሮች ቦርድ እጩ አባላትን ጥቆማ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ መመሪያ ቁጥር SIB/32/2012 እና SIB/48/2019፤ እንዲሁም በኩባንያው የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ጥቆማና ምርጫ የአሰራር ደንብ መሰረት ከሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ መስከረም 14 ቀን 2016 ዓ.ም ብቻ የሚቀበል ሲሆን፤ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟላ ዕጩ የቦርድ አባላትን እንድትጠቁሙ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
ሀ. ቢያንስ 75% የሚሆኑት የመጀመሪያ ዲግሪ ወይም ተመጣጣኝ የትምህርት ደረጃ እውቅና ካለው የትምህርት ተቋም ያጠናቀቁ መሆን ይኖርባቸዋል፤
ለ. የቀሩት 25% እንዳስፈላጊነቱ ቢያንስ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ወይም ተመጣጣኝ የትምህርት ደረጃ ያጠናቀቁ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
ማሳሰቢያ
***የፀሐይ ኢንሹራንስ የዳይሬክተሮች ቦርድ የምልመላና አስመራጭ ኮሚቴ***
ፀሐይ ኢንሹራንስ አክሲዮን ማህበር
የባለአክሲዮኖች 11ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ
የስብሰባ ጥሪ
ለፀሐይ ኢንሹራንስ አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ
በኢትዮጵያ ንግድ ህግ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 አንቀፅ 366(1)፣ 367፣ 393፣ 394 እና በኩባንያዉ መተዳደሪያ ደንብ አንቀፅ 9 መሰረት የፀሐይ ኢንሹራንስ አክሲዮን ማህበር የባለአክሲዮኖች 11ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ታህሳስ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ኢትዮጵያ ሆቴል ይካሄዳል፡፡ ስለሆነም የኩባንያዉ ባለአክሲዮኖች በእለቱ በቦታዉ ተገኝተዉ እንዲሳተፉ የዳይሬክተሮች ቦርድ ጥሪዉን በአክብሮት ያስተላልፋል፡፡
የ11ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎች፤
ዋና ምዝገባ ቁጥር MT/AA/3/0017159/2004
የተከፈለ ካፒታል 292.10 ሚሊዮን
አዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 የቤት ቁጥር 2185 ስ.ቁ.0116506630/38
ማሳሰቢያ፡
የፀሐይ ኢንሹራንስ አክሲዮን ማህበር የዳይሬክተሮች ቦርድ
ፀሐይ ለሁሉም ታበራለች!!!